ይህ ስብስብ ሥራ ነው፡፡ አስከዛሬ ባጫጭር ልቦለዶችና በኖቭሌቶች ወግ የሠራኋቸው፣ የዝርው ሥነ ጽሑፍ ሥራዎቼ ስብስብ ነው፡፡ በዘመን፣ በጭብጥና በቅርጽ የተለያዩ በመሆናቸው ትውስባዊ ፍጥርታቸው የጋራ መለያቸው ነው፡፡ ሕይወትና ሞት (1975)፣ የማለዳ ስንቅ (1980)፣ መቆያ (1980)፣ ቅንጣት (2008) የታተሙ ሲሆን፣ ባባደፋርና (1978) በነገ ተስፋ (2006) የጋራ ስብስብ ሥራዎች ውስጥ አንዳንድ ዘለላ ያጫጭር ልቦለድ ሥራዎቼ ይገኛሉ፡፡ እኒህ ቀዳሚ ሥራዎቼ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲና በሌሎችም ዩኒቨርስቲዎች፣ ኮሌጆችና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላማርኛ ሥነ ጽሑፍ ማስተማሪያነት አጋዥ መጻሕፍት ሁነው ለረዥም ዘመናት አገልግለዋል፡፡ >፣ > እና >ን የመሳሰሉት ገጸ ባሕሪያት ካንባቢያን ሕሊና ውስጥ ስላልጠፉ ናፋቂያቸው ብዙ ነው፡፡ እናም ለትምህርት ማእከሎችም ሆነ ለመላው አንባብያን የይታተሙልን ጥያቄ ምላሽ ይሆናል የሚል እምነት አለኝ፡፡ በስብስቦቹ ውስጥ የነበሩት ግጥሞችም እራሳቸውን ችለው በሌላ መድብል ለብቻቸው የሚታተሙ ይሆናሉ፡፡ ደራሲው
Hinweis: Dieser Artikel kann nur an eine deutsche Lieferadresse ausgeliefert werden.
Hinweis: Dieser Artikel kann nur an eine deutsche Lieferadresse ausgeliefert werden.